መዝሙር 74:1-23

  • አምላክ ሕዝቡን እንዲያስታውስ የቀረበ ጸሎት

    • አምላክ ያከናወናቸው የማዳን ሥራዎች (12-17)

    • ‘ጠላት እንደተሳለቀ አስብ’ (18)

ማስኪል።* የአሳፍ+ መዝሙር። 74  አምላክ ሆይ፣ ለዘላለም የጣልከን ለምንድን ነው?+ በመስክህ በተሰማራው መንጋ ላይ ቁጣህ የነደደው* ለምንድን ነው?+   ከረጅም ዘመን በፊት የራስህ ያደረግከውን ሕዝብ፣*+ርስትህ አድርገህ የዋጀኸውን ነገድ አስታውስ።+ የኖርክበትን የጽዮን ተራራ+ አስብ።   ለዘለቄታው ወደፈራረሰው ቦታ አቅና።+ ጠላት በቅዱሱ ስፍራ ያለውን ነገር ሁሉ አጥፍቷል።+   ጠላቶችህ በመሰብሰቢያ ቦታህ* ውስጥ በድል አድራጊነት ጮኹ።+ በዚያም የራሳቸውን ዓርማ ምልክት አድርገው አቆሙ።   መጥረቢያቸውን ይዘው ጥቅጥቅ ያሉ ደኖችን እንደሚጨፈጭፉ ሰዎች ናቸው።   በቅርጻ ቅርጾች ያጌጡትን+ ግድግዳዎች በጠቅላላ በመጥረቢያና በብረት ዘንግ አፈራረሱ።   መቅደስህን በእሳት አቃጠሉ።+ ስምህ የተጠራበትን የማደሪያ ድንኳን መሬት ላይ ጥለው አረከሱት።   እነሱም ሆኑ ዘሮቻቸው በልባቸው “በምድሪቱ ላይ ያሉት የአምላክ መሰብሰቢያ* ቦታዎች በሙሉ ይቃጠሉ” ብለዋል።   የምናያቸው ምልክቶች የሉም፤አንድም የቀረ ነቢይ የለም፤ደግሞም ይህ እስከ መቼ እንደሚቀጥል ከእኛ መካከል የሚያውቅ የለም። 10  አምላክ ሆይ፣ ባላጋራ የሚሳለቀው እስከ መቼ ነው?+ ጠላት ስምህን ለዘላለም እያቃለለ ይኖራል?+ 11  እጅህን ይኸውም ቀኝ እጅህን የሰበሰብከው ለምንድን ነው?+ እጅህን ከጉያህ* አውጥተህ አጥፋቸው። 12  ይሁንና በምድር ላይ ታላቅ የማዳን ሥራ የሚፈጽመው አምላክከጥንት ጀምሮ ንጉሤ ነው።+ 13  በብርታትህ ባሕሩን አናወጥክ፤+በውኃ ውስጥ ያሉትን ግዙፍ የባሕር ፍጥረታት ራስ ሰባበርክ። 14  የሌዋታንን* ራሶች አደቀቅክ፤በበረሃ ለሚኖሩት ሰዎች ምግብ አድርገህ ሰጠሃቸው። 15  ለምንጮችና ለጅረቶች መውጫ ያበጀኸው አንተ ነህ፤+ሳያቋርጡ የሚፈስሱትን ወንዞች አደረቅክ።+ 16  ቀኑ የአንተ ነው፤ ሌሊቱም የአንተ ነው። ብርሃንንና ፀሐይን* ሠራህ።+ 17  የምድርን ወሰኖች ሁሉ ደነገግክ፤+በጋና ክረምት እንዲፈራረቁ አደረግክ።+ 18  ይሖዋ ሆይ፣ ጠላት እንደተሳለቀ፣ሞኝ ሕዝብ ስምህን እንዴት እንዳቃለለ አስብ።+ 19  የዋኖስህን ሕይወት* ለዱር አራዊት አትስጥ። የተጎሳቆለውን ሕዝብህን ሕይወት ለዘላለም አትርሳ። 20  ቃል ኪዳንህን አስብ፤በምድሪቱ ላይ ያሉት ጨለማ ቦታዎች የዓመፅ መናኸሪያ ሆነዋልና። 21  የተደቆሰው ሰው አዝኖ አይመለስ፤+ችግረኛውና ድሃው ስምህን ያወድስ።+ 22  አምላክ ሆይ፣ ተነስ፤ ደግሞም ለራስህ ተሟገት። ሞኝ ሰው ቀኑን ሙሉ እንዴት እንደሚሳለቅብህ አስብ።+ 23  ጠላቶችህ የሚሉትን አትርሳ። አንተን የሚዳፈሩ ሰዎች የሚያሰሙት ሁካታ ያለማቋረጥ ወደ ላይ እየወጣ ነው።

የግርጌ ማስታወሻዎች

ቃል በቃል “የጨሰው።”
ቃል በቃል “ጉባኤ።”
ወይም “ጉባኤ በምታደርግበት ቦታ።”
ወይም “አምላክ የሚመለክባቸው።”
ወይም “ከልብስህ እጥፋት።”
ወይም “ብርሃን ሰጪ አካልንና ፀሐይን።”
ወይም “ነፍስ።”