መዝሙር 100:1-5

  • ፈጣሪን ማመስገን

    • “ይሖዋን በደስታ አገልግሉት” (2)

    • ‘የሠራን አምላክ ነው’ (3)

የምስጋና ማህሌት። 100  ምድር ሁሉ፣ በድል አድራጊነት ለይሖዋ እልል በሉ።+  2  ይሖዋን በደስታ አገልግሉት።+ በእልልታ ወደ ፊቱ ቅረቡ።  3  ይሖዋ፣ አምላክ መሆኑን እወቁ።*+ የሠራን እሱ ነው፤ እኛም የእሱ ንብረት ነን።*+ እኛ ሕዝቡና የማሰማሪያው በጎች ነን።+  4  በምስጋና ወደ በሮቹ፣በውዳሴም ወደ ቅጥር ግቢዎቹ ግቡ።+ ምስጋና አቅርቡለት፤ ስሙንም አወድሱ።+  5  ይሖዋ ጥሩ ነውና፤+ታማኝ ፍቅሩ ለዘላለም፣ታማኝነቱም ከትውልድ እስከ ትውልድ ጸንቶ ይኖራል።+

የግርጌ ማስታወሻዎች

ወይም “እውቅና ስጡ።”
“እኛም አይደለንም” ማለትም ሊሆን ይችላል።