መዝሙር 93:1-5

  • ግርማ የተላበሰው የይሖዋ አገዛዝ

    • “ይሖዋ ነገሠ!” (1)

    • ‘ማሳሰቢያዎችህ አስተማማኝ ናቸው’ (5)

93  ይሖዋ ነገሠ!+ ግርማ ተጎናጽፏል፤ይሖዋ ብርታት ለብሷል፤እንደ ቀበቶ ታጥቆታል። ምድር* በጽኑ ተመሥርታለች፤ልትናወጥ አትችልም።  2  ዙፋንህ ከብዙ ዘመናት በፊት ጸንቶ የተመሠረተ ነው፤+አንተ ከዘላለም እስከ ዘላለም አለህ።+  3  ይሖዋ ሆይ፣ ወንዞቹ ጎረፉ፤ወንዞቹ ጎረፉ፤ አስገመገሙም፤ወንዞቹ ይጎርፋሉ፤ ደግሞም በኃይል ይላተማሉ።  4  ከብዙ ውኃዎች ድምፅ፣ኃይለኛ ከሆነው የባሕር ማዕበልም በላይ፣+ይሖዋ ከፍ ባለ ቦታ ግርማ ተጎናጽፏል።+  5  ማሳሰቢያዎችህ እጅግ አስተማማኝ ናቸው።+ ይሖዋ ሆይ፣ ቤትህ ለዘላለሙ በቅድስና ያጌጠ ነው።*+

የግርጌ ማስታወሻዎች

ወይም “ፍሬያማ የሆነችው ምድር።”
ወይም “ቅድስና ይገባዋል።”