በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ጥያቄ 18

ወደ አምላክ መቅረብ የምትችለው እንዴት ነው?

 “ጸሎት ሰሚ የሆንከው አምላክ ሆይ፣ ሁሉም ዓይነት ሰው ወደ አንተ ይመጣል።”

መዝሙር 65:2

 “በሙሉ ልብህ በይሖዋ ታመን፤ ደግሞም በገዛ ራስህ ማስተዋል አትመካ። በመንገድህ ሁሉ እሱን ግምት ውስጥ አስገባ፤ እሱም ጎዳናህን ቀና ያደርገዋል።”

ምሳሌ 3:5, 6

 “የዘላለም ሕይወት ማግኘት እንዲችሉ ብቸኛው እውነተኛ አምላክ የሆንከውን አንተንና የላክኸውን ኢየሱስ ክርስቶስን ማወቅ አለባቸው።”

ዮሐንስ 17:3

 “[አምላክ] ከእያንዳንዳችን የራቀ . . . አይደለም።”

የሐዋርያት ሥራ 17:27

 “ፍቅራችሁ ከአምላክ ፈቃድ ትክክለኛ እውቀትና ጥልቅ ግንዛቤ ጋር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ እንዲሄድ መጸለዬን እቀጥላለሁ።”

ፊልጵስዩስ 1:9

 “ከእናንተ መካከል ጥበብ የጎደለው ሰው ካለ አምላክን ያለማሰለስ ይለምን፤ አምላክ ማንንም ሳይነቅፍ ለሁሉም በልግስና ይሰጣልና፤ ይህም ሰው ይሰጠዋል።”

ያዕቆብ 1:5

 “ወደ አምላክ ቅረቡ፤ እሱም ወደ እናንተ ይቀርባል። እናንተ ኃጢአተኞች እጆቻችሁን አንጹ፤ እናንተ ወላዋዮች ልባችሁን አጥሩ።”

ያዕቆብ 4:8

 “አምላክን መውደድ ማለት ትእዛዛቱን መጠበቅ ማለት ነውና፤ ትእዛዛቱ ደግሞ ከባድ አይደሉም።”

1 ዮሐንስ 5:3