በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችና ማብራሪያቸው

በሰፊው የሚታወቁ አንዳንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅሶችንና አባባሎችን ትክክለኛ ትርጉም እንድታነብ እንጋብዝሃለን። የጥቅሶቹን አውድ በማጤን ጥቅሶቹ የተጻፉበትን ዓላማ ማወቅ ትችላለህ። ተጨማሪ ማብራሪያ የሚሰጡት የግርጌ ማስታወሻዎችና ማጣቀሻዎች ግንዛቤህን ለማስፋት ይረዱሃል።

የዘፍጥረት 1:1 ማብራሪያ—“በመጀመሪያ አምላክ ሰማያትንና ምድርን ፈጠረ”

የመጽሐፍ ቅዱስ መክፈቻ የሆነው ይህ ጥቅስ የትኞቹን ሁለት ወሳኝ እውነቶች ይዟል?

የዘፀአት 20:12 ማብራሪያ—“አባትህንና እናትህን አክብር”

አምላክ ይህን ትእዛዝ የሚፈጽሙ ሰዎች ዕድሜያቸው እንደሚረዝም ቃል ገብቷል፤ ይህም ትእዛዙን ለመፈጸም የሚያነሳሳ ተጨማሪ ምክንያት ይሆናል።

የኢያሱ 1:9 ማብራሪያ—“ጽና፣ አይዞህ”

ተፈታታኝ ሁኔታዎችና የሚታለፉ የማይመስሉ እንቅፋቶች ሲያጋጥሙህ ድፍረትና ጥንካሬ ማግኘት የምትችለው እንዴት ነው?

የመዝሙር 23:4 ማብራሪያ—“በሞት ጥላ መካከል እንኳ ብሄድ”

የአምላክ አገልጋዮች እንደ ድቅድቅ ጨለማ ያለ ችግር በሚያጋጥማቸው ጊዜም እንኳ የአምላክን እንክብካቤ የሚያዩት እንዴት ነው?

የመዝሙር 37:4 ማብራሪያ—“በእግዚአብሔር ደስ ይበልህ”

ይህ መዝሙር ጥበብ ለማግኘትና አምላክ የሚደሰትባቸው ዓይነት ሰዎች ለመሆን የሚረዳን እንዴት ነው?

የመዝሙር 46:10 ማብራሪያ—“ዕረፉ፣ እኔም አምላክ እንደ ሆንሁ እወቁ”

ይህ ጥቅስ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጸጥ ብሎ ስለ መቀመጥ ነው የሚናገረው?

የምሳሌ 3:5, 6 ማብራሪያ—“በገዛ ራስህ ማስተዋል አትመካ”

ከራስህ ይልቅ በአምላክ እንደምትታመን ማሳየት የምትችለው እንዴት ነው?

የምሳሌ 16:3 ማብራሪያ—“የምታደርገውን ሁሉ ለእግዚአብሔር ዐደራ ስጥ”

ሰዎች ውሳኔ ከማድረጋቸው በፊት የአምላክን መመሪያ ለማግኘት ጥረት ማድረጋቸው አስፈላጊ የሆነባቸው ሁለት ምክንያቶች የትኞቹ ናቸው?

የምሳሌ 17:17 ማብራሪያ​—“ወዳጅ ምንጊዜም ወዳጅ ነው”

በምሳሌ መጽሐፍ ውስጥ የሚገኘው ይህ አገላለጽ፣ እውነተኛ ወዳጅነት ምን እንደሆነ ውብ በሆኑ ቃላት ይገልጻል።

የምሳሌ 22:6 ማብራሪያ—“ልጅን ሊሄድበት በሚገባው መንገድ አሠልጥነው”

ልጅ ሊሄድበት የሚገባው “መንገድ” ምንድን ነው? ይህ መንገድ እንደ እያንዳንዱ ሰው ሁኔታ ይለያያል?

የመክብብ 3:11 ማብራሪያ—“ሁሉንም ነገር በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው”

ውብ የሆኑት የአምላክ ሥራዎች የፈጠራቸው ነገሮች ብቻ አይደሉም። ይህን ማወቅህ ለውጥ ያመጣል?

የኢሳይያስ 26:3 ማብራሪያ—“በአንተ ለምትደገፍ ነፍስ ፈጽመህ በሰላም ትጠብቃታለህ”

በእርግጥ ፍጹም ሰላም ማግኘት ይቻላል? በአምላክ መደገፍ ሲባል ምን ማለት ነው?

የኢሳይያስ 40:31 ማብራሪያ—‘ይሖዋን ተስፋ የሚያደርጉ ኃይላቸው ይታደሳል’

መጽሐፍ ቅዱስ ከአምላክ ብርታት የሚያገኝን ሰው እየበረረ ወደ ላይ ከሚወጣ ንስር ጋር የሚያመሳስለው ለምንድን ነው?

የኢሳይያስ 41:10 ማብራሪያ—“እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ”

ይሖዋ ታማኝ አገልጋዮቹን እንደሚደግፍ ለማረጋገጥ ሦስት አገላለጾችን ተጠቅሟል።

የኢሳይያስ 42:8 ማብራሪያ—“እኔ እግዚአብሔር ነኝ”

አምላክ ለራሱ ያወጣው ስም ማን ነው?

የኤርምያስ 11:11 ማብራሪያ​—“ክፉ ነገር አመጣባቸዋለሁ”

አምላክ በእርግጥ በሕዝቡ ላይ “ክፉ ነገር” አምጥቶባቸዋል? ወይስ ይህ አገላለጽ የሚያመለክተው እንዲህ ያለ ነገር እንዲደርስባቸው መፍቀዱን ብቻ ነው?

የኤርምያስ 29:11 ማብራሪያ—“ለእናንተ ያለኝን ዕቅድ እኔ ዐውቃለሁ”

አምላክ ለእያንዳንዱ ሰው የተወሰነ ዕቅድ አለው?

የኤርምያስ 33:3 ማብራሪያ—“ጥራኝ፤ እኔም እመልስልሃለሁ”

አምላክ ይህን ግብዣ ለሚቀበሉ ሁሉ “ታላቅና ለመረዳት አዳጋች የሆነ ነገር” እንደሚገልጥላቸው ቃል ገብቷል። ይህ ምንድን ነው? አምላክ በዛሬው ጊዜም እንዲህ ያደርጋል?

የሚክያስ 6:8 ማብራሪያ—“በአምላክህም ፊት በትሕትና ትራመድ ዘንድ”

በዚህ ጥቅስ ላይ አምላክ ከእኛ የሚፈልገው ነገር በሦስት ሐረጎች ቁልጭ ተደርጎ ተቀምጧል።

የማቴዎስ 6:33 ማብራሪያ—“ከሁሉ አስቀድማችሁ የአምላክን መንግሥት . . . ፈልጉ”

ኢየሱስ ይህን ሲል ክርስቲያኖች መተዳደሪያ ለማግኘት መሥራት እንደማያስፈልጋቸው መናገሩ ነው?

የማቴዎስ 6:34 ማብራሪያ—‘ስለ ነገ አትጨነቁ’

ማቴዎስ 6:34 በአዲስ ዓለም ትርጉምና በአዲሱ መደበኛ ትርጉም ላይ እንዴት እንደተተረጎመ አንብብ፤ እንዲሁም ተጨማሪ ማብራሪያ ለማግኘት የጥቅሱን አውድና ማጣቀሻዎቹን ተመልከት። ይህ የመጽሐፍ ቅዱስ ጥቅስ ምን ትርጉም እንዳለው መርምር።

የማቴዎስ 11:28-30 ማብራሪያ—“ወደ እኔ ኑ፣ እኔም አሳርፋችኋለሁ”

ኢየሱስ አድማጮቹ ከሚደርስባቸው ጭቆናና ግፍ ወዲያውኑ እንደሚገላገሉ መግለጹ ነው?

የማርቆስ 1:15 ማብራሪያ—“የአምላክ መንግሥት ቀርቧል”

ኢየሱስ የአምላክ መንግሥት በዚያ ጊዜ መግዛት እንደጀመረ መናገሩ ነበር

የማርቆስ 11:24 ማብራሪያ—“የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ”

ኢየሱስ እምነትንና ጸሎትን አስመልክቶ የሰጠው ምክር በዛሬው ጊዜ ተፈታታኝ ሁኔታዎችን ለመወጣት የሚረዳን እንዴት ነው?

የሉቃስ 1:37 ማብራሪያ—“ለእግዚአብሔር የሚሳነው ነገር የለምና”

ሁሉን ቻይ የሆነው አምላክ፣ የገባውን ቃል ከመፈጸም ሊያግደው የሚችል ምንም ነገር የለም። ይህ ለአንተ ምን ትርጉም አለው?

የሉቃስ 2:14 ማብራሪያ—“ሰላምም እርሱ ለሚወዳቸው ሰዎች በምድር ይሁን”

እነዚህ ቃላት በዛሬው ጊዜ ላሉ ሰዎች ምን ትርጉም አላቸው?

የዮሐንስ 1:1 ማብራሪያ—“በመጀመሪያ ቃል ነበረ”

ይህ ጥቅስ ኢየሱስ ክርስቶስ ሰው ሆኖ ወደ ምድር ከመምጣቱ በፊት ስላሳለፈው ሕይወት መረጃ ይሰጠናል።

የዮሐንስ 3:16 ማብራሪያ—“ዓለምን እንዲሁ ወዶአልና”

ይሖዋ አምላክ እያንዳንዳችንን እንደሚወደንና የዘላለም ሕይወት እንድናገኝ እንደሚፈልግ ያሳየው እንዴት ነው?

የዮሐንስ 14:6 ማብራሪያ—“እኔ መንገድ፣ እውነትና ሕይወት ነኝ”

ይሖዋን ማምለክ የሚፈልግ ሰው ኢየሱስ ያለውን ወሳኝ ሚና መገንዘብ የሚያስፈልገው ለምንድን ነው?

የዮሐንስ 14:27 ማብራሪያ—“ሰላምን እተውላችኋለሁ”

ኢየሱስ ለእውነተኛ ተከታዮቹ የተወላቸው ወይም የሰጣቸው ምን ዓይነት ሰላም ነው? ይህን ሰላም ማግኘት የምንችለው እንዴት ነው?

የዮሐንስ 15:13 ማብራሪያ—“የበለጠ ፍቅር ያለው ማንም የለም”

የኢየሱስ ተከታዮች የእሱን ፍቅር መኮረጅ የሚችሉት እንዴት ነው?

የዮሐንስ 16:33 ማብራሪያ—“እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ”

የኢየሱስ ቃላት ተከታዮቹ አምላክን ማስደሰት እንደሚችሉ የሚያረጋግጡት እንዴት ነው?

የሐዋርያት ሥራ 1:8 ማብራሪያ—“ኃይል ትቀበላላችሁ”

ኢየሱስ ለተከታዮቹ ቃል የገባላቸው ኃይል ምንድን ነው? ይህ ኃይል ምን እንዲያደርጉስ ይረዳቸዋል?

የሮም 5:8 ማብራሪያ—‘ገና ኃጢአተኞች ሳለን ክርስቶስ ሞቶልናል’

ሰዎች ኃጢአተኛ ስለሆኑ አስተሳሰባቸውንና ድርጊታቸውን ከአምላክ የጽድቅ መሥፈርቶች ጋር ማስማማት ይከብዳቸዋል። ታዲያ ከአምላክ ጋር ጥሩ ዝምድና መመሥረትና ወደፊት የዘላለም ሕይወት ማግኘት የሚችሉት እንዴት ነው?

የሮም 6:23 ማብራሪያ—“የኀጢአት ደመወዝ ሞት ነውና፤ የእግዚአብሔር ስጦታ ግን . . . የዘላለም ሕይወት ነው”

ኃጢአተኛ የሆነ ሰው በራሱ ጥረት መዳን ሊያገኝ አይችልም፤ ሆኖም አምላክ የሚሰጠንን የዘላለም ሕይወት ስጦታ ማግኘት እንችላለን። እንዴት?

የሮም 10:13 ማብራሪያ—“የጌታን ስም የሚጠራ”

አምላክ ብሔር፣ ጎሳ ወይም የኑሮ ደረጃ ሳይለይ ለሁሉም ሰዎች መዳን የሚችሉበትና የዘላለም ሕይወት የሚያገኙበት አጋጣሚ ከፍቷል።

የሮም 12:2 ማብራሪያ—“በአእምሮአችሁ መታደስ ተለወጡ”

አምላክ ሰዎች ለውጥ እንዲያደርጉ ያስገድዳል?

የሮም 12:12 ማብራሪያ—“በተስፋ ደስተኞች ሁኑ፤ በመከራ ታገሡ፤ በጸሎት ጽኑ”

ክርስቲያኖች ስደትም ሆነ ሌሎች ችግሮች ሲደርሱባቸው በታማኝነት ለመጽናት ምን ይረዳቸዋል?

የሮም 15:13 ማብራሪያ—“የተስፋ አምላክ ደስታንና ሰላምን ሁሉ ይሙላባችሁ”

ሰላም እና ፍቅር ከተስፋ እና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ምን ተያያዥነት አላቸው?

የ1 ቆሮንቶስ 10:13 ማብራሪያ— “እግዚአብሔር ታማኝ ነው”

ስህተት የሆነ ነገር ለማድረግ ስንፈተን አምላክ ታማኝ መሆኑ የሚጠቅመን በየትኞቹ መንገዶች ነው?

የ2 ቆሮንቶስ 12:9 ማብራሪያ—“ጸጋዬ ይበቃሃል”

የአምላክ ጸጋ ሐዋርያው ጳውሎስን በእጅጉ የጠቀመው እንዴት ነው? እኛስ ተጠቃሚ መሆን የምንችለው እንዴት ነው?

የገላትያ 6:9 ማብራሪያ—“መልካም ሥራን ለመሥራት አንታክት”

መልካም ማድረጋቸውን የሚቀጥሉ ክርስቲያኖች ምን ውጤት ያገኛሉ?

ኤፌሶን 3:20—“ከምንለምነው ወይም ከምናስበው ሁሉ በላይ እጅግ አብልጦ ማድረግ [የሚቻለው]” አምላክ

አምላክ የአገልጋዮቹን ጸሎት የሚመልሰውና የልባቸውን መሻት የሚፈጽመው እንዴት ነው?

የፊልጵስዩስ 4:6, 7 ማብራሪያ—“ስለ ምንም ነገር አትጨነቁ”

የአምላክ አገልጋዮች፣ ከጭንቀታቸው እፎይ እንዲሉና ውስጣዊ ሰላም እንዲያገኙ የሚረዷቸው የጸሎት ዓይነቶች የትኞቹ ናቸው?

የፊልጵስዩስ 4:13 ማብራሪያ—“ኃይልን በሚሰጠኝ በክርስቶስ ሁሉን እችላለሁ”

ሐዋርያው ጳውሎስ “ለሁሉም ነገር የሚሆን” ኃይል እንደሚያገኝ ሲናገር ምን ማለቱ ነበር?

የቆላስይስ 3:23 ማብራሪያ—“የምታደርጉትን ሁሉ . . . በሙሉ ልባችሁ አድርጉት”

አንድ ክርስቲያን ሥራውን የሚያከናውንበት መንፈስ ከአምላክ ጋር ያለውን ዝምድና የሚነካው እንዴት ነው?

የ2 ጢሞቴዎስ 1:7 ማብራሪያ—‘አምላክ የፍርሃት መንፈስ አልሰጠንም’

አምላክ አንድ ሰው ፍርሃቱን እንዲያሸንፍና በድፍረት ትክክለኛውን ነገር እንዲያደርግ የሚረዳው እንዴት ነው?

የዕብራውያን 4:12 ማብራሪያ—“የእግዚአብሔር ቃል ሕያውና የሚሠራ ነው”

የአምላክ ቃል በአንተ ሕይወት ውስጥ እንዲሠራ ትፈቅዳለህ? ይህ ስለ አንተ ምን ይናገራል?

የ1 ጴጥሮስ 5:6, 7 ማብራሪያ—“ራሳችሁን ዝቅ አድርጉ፤ . . . የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት”

የሚያስጨንቀንን ነገር በአምላክ ላይ “መጣል” ሲባል ምን ማለት ነው? ይህን ማድረግ የሚያረጋጋንስ እንዴት ነው?

የራእይ 21:1 ማብራሪያ—“አዲስ ሰማይና አዲስ ምድር”

መጽሐፍ ቅዱስ የዚህን ጥቅስ ትርጉም በተመለከተ ምን ፍንጭ ይሰጠናል?

የራእይ 21:4 ማብራሪያ—“እንባዎችንም ሁሉ ከዓይኖቻቸው ያብሳል”

ይህ ጥቅስ የወደፊቱን ጊዜ በተመለከተ አስደሳች ተስፋ ይሰጣል።