መዝሙር 67:1-7

  • የምድር ዳርቻዎች አምላክን ይፈራሉ

    • የአምላክ መንገድ ይታወቃል (2)

    • “ሕዝቦች ሁሉ ያወድሱህ” (3,5)

    • “አምላክ ይባርከናል” (6, 7)

ለሙዚቀኞች ቡድን መሪ፤ በባለ አውታር መሣሪያዎች የሚታጀብ። ማህሌት። መዝሙር። 67  አምላክ ሞገስ ያሳየናል፤ ደግሞም ይባርከናል፤ፊቱን በእኛ ላይ ያበራል፤+ (ሴላ)  2  ይህም መንገድህ በምድር ሁሉ ላይ፣+የማዳን ሥራህም በብሔራት ሁሉ መካከል እንዲታወቅ ነው።+  3  አምላክ ሆይ፣ ሕዝቦች ያወድሱህ፤አዎ፣ ሕዝቦች ሁሉ ያወድሱህ።  4  ብሔራት ሐሴት ያድርጉ፤ እልልም ይበሉ፤+በሕዝቦች ላይ በትክክል ትፈርዳለህና።+ የምድርን ብሔራት ትመራቸዋለህ። (ሴላ)  5  አምላክ ሆይ፣ ሕዝቦች ያወድሱህ፤ሕዝቦች ሁሉ ያወድሱህ።  6  ምድር ፍሬዋን ትሰጣለች፤+አምላክ፣ አዎ፣ አምላካችን ይባርከናል።+  7  አምላክ ይባርከናል፤የምድር ዳርቻዎችም ሁሉ ይፈሩታል።*+

የግርጌ ማስታወሻዎች

ወይም “ያከብሩታል።”