መዝሙር 129:1-8

  • አጠቁኝ፤ ሊያሸንፉኝ ግን አልቻሉም

    • ጽዮንን የሚጠሉ ሁሉ ኀፍረት ይከናነባሉ (5)

ወደ ላይ የመውጣት መዝሙር። 129  “ከወጣትነቴ ጀምሮ ሁልጊዜ ያጠቁኝ ነበር”፤+ እስራኤል እንዲህ ይበል፦  2  “ከወጣትነቴ ጀምሮ ሁልጊዜ ያጠቁኝ ነበር፤+ሆኖም ሊያሸንፉኝ አልቻሉም።+  3  አራሾች ጀርባዬን አረሱት፤+ትልማቸውንም አስረዘሙት።”*  4  ይሖዋ ግን ጻድቅ ነው፤+የክፉዎችን ገመድ በጣጥሷል።+  5  ጽዮንን የሚጠሉ ሁሉ፣ኀፍረት ይከናነባሉ፤ ተዋርደውም ወደኋላቸው ይመለሳሉ።+  6  ከመነቀሉ በፊት እንደሚጠወልግ፣በጣሪያ ላይ እንደበቀለ ሣር ይሆናሉ፤  7  እንዲህ ዓይነቱ ሣር የአጫጁን እጅ፣ነዶ የሚሰበስበውንም ሰው ክንዶች ሊሞላ አይችልም።  8  በዚያ የሚያልፉ ሰዎች “የይሖዋ በረከት በእናንተ ላይ ይሁን፤በይሖዋ ስም እንባርካችኋለን” አይሉም።

የግርጌ ማስታወሻዎች

ይህ ጠላቶቻቸው የሚፈጽሙባቸውን የጭካኔ ድርጊት ያሳያል።