በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ክፍል 5

ኢየሱስ ከዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ ያከናወነው አገልግሎት

“ብዙዎች በእሱ አመኑ።”—ዮሐንስ 10:42

ኢየሱስ ከዮርዳኖስ በስተ ምሥራቅ ያከናወነው አገልግሎት

በዚህ ክፍል ውስጥ

ምዕራፍ 82

ኢየሱስ በፔሪያ ያከናወነው አገልግሎት

ኢየሱስ፣ መዳን ለማግኘት ምን እንደሚያስፈልግ ለአድማጮቹ አብራራ። ምክሩ በዚያ ዘመን ጠቃሚ ነበር። ዛሬስ?

ምዕራፍ 83

ግብዣ—አምላክ የሚጋብዘው እነማንን ነው?

ኢየሱስ በአንድ ፈሪሳዊ ቤት እየተመገበ እያለ ስለ አንድ ታላቅ የራት ግብዣ ምሳሌ ተናገረ። ለሁሉም የአምላክ ሕዝቦች የሚሆን ጠቃሚ ትምህርት ሰጥቷል። ትምህርቱ ምንድን ነው?

ምዕራፍ 84

ደቀ መዝሙር መሆን ምን ያህል ከባድ ኃላፊነት ነው?

የክርስቶስ ደቀ መዝሙር መሆን ከባድ ኃላፊነት ነው። ኢየሱስ፣ የእሱ ደቀ መዝሙር መሆን ምን እንደሚጠይቅ በግልጽ ተናግሯል። ተከታዮቹ ሊሆኑ ያሰቡ አንዳንዶች በተናገረው ነገር ደንግጠው ይሆናል።

ምዕራፍ 85

ንስሐ በሚገባ ኃጢአተኛ መደሰት

ጸሐፍትና ፈሪሳውያን፣ ኢየሱስ ከተራው ሰው ጋር በመቀራረቡ ተቹት። ኢየሱስም አምላክ ኃጢአተኞችን እንዴት እንደሚመለከታቸው ለማሳየት ምሳሌዎች ተናገረ።

ምዕራፍ 86

ጠፍቶ የነበረው ልጅ ተመለሰ

ኢየሱስ ስለ አባካኙ ልጅ ከተናገረው ምሳሌ ምን እንማራለን?

ምዕራፍ 87

አርቆ በማሰብ ዕቅድ ማውጣት

ኢየሱስ፣ ተንኮለኛና ሙሰኛ የሆነን የቤት አስተዳዳሪ ምሳሌ በመጠቀም አንድ አስገራሚ ሐቅ አስተማረ።

ምዕራፍ 88

የሀብታሙ ሰውና የአልዓዛር ሁኔታ ተለወጠ

የኢየሱስን ምሳሌ ለመረዳት ቁልፉ፣ ሁለቱ ዋነኛ ገጸ ባሕርያት እነማንን እንደሚያመለክቱ ማወቅ ነው።

ምዕራፍ 89

ወደ ይሁዳ ሲጓዝ በፔሪያ አስተማረ

ኢየሱስ ደጋግመው የበደሉንንም እንኳ ይቅር ለማለት የሚረዳንን ባሕርይ ጎላ አድርጎ ገልጿል።

ምዕራፍ 90

“ትንሣኤና ሕይወት”

ኢየሱስ በእሱ ‘የሚያምን ሁሉ ፈጽሞ እንደማይሞት’ ሲናገር ምን ማለቱ ነው?

ምዕራፍ 91

አልዓዛር ከሞት ተነሳ

ከአልዓዛር ትንሣኤ ጋር የተያያዙ ሁለት ቁልፍ ነገሮች የኢየሱስ ተቃዋሚዎች እንኳ ይህን ተአምር መካድ እንዳይችሉ አድርገዋል።

ምዕራፍ 92

የሥጋ ደዌ የነበረበት ሰው አመስጋኝነት አሳየ

የተፈወሰው ሰው ኢየሱስን ብቻ ሳይሆን አምላክንም አመስግኗል።

ምዕራፍ 93

የሰው ልጅ ይገለጣል

የክርስቶስ መገኘት ከመብረቅ ጋር የሚመሳሰለው እንዴት ነው?

ምዕራፍ 94

ሁለት አስፈላጊ ነገሮች—ጸሎትና ትሕትና

ኢየሱስ ስለ ክፉው ዳኛ እና ስለ አንዲት መበለት በተናገረው ምሳሌ ላይ አንድን ባሕርይ አጉልቷል።

ምዕራፍ 95

ስለ ፍቺና ልጆችን ስለ መውደድ የተሰጠ ትምህርት

ኢየሱስ ለትናንሽ ልጆች ያለው አመለካከት ከደቀ መዛሙርቱ በጣም የተለየ ነው። ለምን?

ምዕራፍ 96

ኢየሱስ ለአንድ ሀብታም አለቃ መልስ ሰጠ

ኢየሱስ፣ ሀብታም ሰው ወደ አምላክ መንግሥት ከሚገባ ግመል በመርፌ ቀዳዳ ቢሾልክ እንደሚቀል የተናገረው ለምንድን ነው?

ምዕራፍ 97

የወይኑ እርሻ ሠራተኞች ምሳሌ

ፊተኞች የሆኑ ብዙዎች ኋለኞች፣ ኋለኞች የሆኑ ደግሞ ፊተኞች የሚሆኑት እንዴት ነው?

ምዕራፍ 98

ሐዋርያት ትልቅ ቦታ እንደሚፈልጉ እንደገና አሳዩ

ያዕቆብና ዮሐንስ በመንግሥቱ ለየት ያለ ቦታ እንዲሰጣቸው ጠየቁ፤ እንዲህ ዓይነት ፍላጎት ያላቸው ግን እነሱ ብቻ አይደሉም።

ምዕራፍ 99

ኢየሱስ ዓይነ ስውሮችን ፈወሰ እንዲሁም ዘኬዎስን ረዳው

ኢየሱስ በኢያሪኮ አቅራቢያ አንድን ዓይነ ስውር ከመፈወሱ ጋር በተያያዘ እርስ በርሱ የሚጋጭ የሚመስለው የመጽሐፍ ቅዱስ ዘገባ እንደማይጋጭ እንዴት ማወቅ እንችላለን?

ምዕራፍ 100

ስለ አሥሩ ምናን የተናገረው ምሳሌ

ኢየሱስ “ላለው ሁሉ ተጨማሪ ይሰጠዋል፤ ከሌለው ሰው ላይ ግን ያው ያለው እንኳ ይወሰድበታል” ሲል ምን ማለቱ ነው?