በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

መዝሙር 99

እልፍ አእላፋት ወንድሞች

እልፍ አእላፋት ወንድሞች

(ራእይ 7:9, 10)

  1. 1. እልፍ አእላፋት ወንድሞች፣

    እጅግ ብዙ ሰዎች፣

    ታማኝ ምሥክር ናቸው

    ጸንተው ባቋማቸው።

    እልፍ አእላፍ ሆነናል፤

    በቁጥር በዝተናል።

    ብሔር፣ ቋንቋ፣ ነገድ ሳይለየን

    ያህን ’ናከብራለን።

  2. 2. እልፍ አእላፋት ወንድሞች፣

    ሁሌም እንሰብካለን፤

    ምሥራች ’ናበስራለን፣

    በየቦታው ሄደን።

    መመሥከር አናቆምም፣

    ድካም ቢሰማንም፤

    ኢየሱስ ለዛሉ ሰላምን፣

    ይሰጣል እፎይታን።

  3. 3. እልፍ አእላፍ ወንድሞችን፣

    አምላክ ይጠብቃል፤

    ቀን ከሌት በመቅደሱ

    ያገለግሉታል።

    እልፍ አእላፍ ሆነናል፤

    እንመሠክራለን፤

    በምድራዊው አደባባይ ላይ

    ከሱ ጋ ’ንሠራለን።

(በተጨማሪም ኢሳ. 52:7⁠ን፣ ማቴ. 11:29⁠ን እና ራእይ 7:15⁠ን ተመልከት።)