በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

4ኛው ቁልፍ፦ መከባበር

4ኛው ቁልፍ፦ መከባበር

4ኛው ቁልፍ፦ መከባበር

“ጩኸትና ስድብ ሁሉ . . . ከእናንተ መካከል ይወገድ።”—ኤፌሶን 4:31

ምን ማለት ነው? ችግር ያለባቸውም ሆኑ የተሳካላቸው ቤተሰቦች አለመግባባት ያጋጥማቸዋል። ይሁን እንጂ የተሳካ የቤተሰብ ሕይወት ያላቸው ቤተሰቦች ስለተነሳው አለመግባባት ሲወያዩ የሽሙጥ ንግግር፣ ስድብና ሌላ ዓይነት የዘለፋ አነጋገሮችን አይጠቀሙም። እያንዳንዱ የቤተሰብ አባል ለራሱ እንዲደረግለት የሚፈልገውን ነገር ለሌላው ያደርጋል።—ማቴዎስ 7:12

አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው? ቃላት አውዳሚ ውጤት የሚያስከትሉ የጦር መሣሪያዎች ሊሆኑ ይችላሉ። አንድ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሳሌ “ከጠበኛና ከቁጡ ሴት ጋር ከመቀመጥ በምድረ በዳ መቀመጥ ይሻላል” ይላል። (ምሳሌ 21:19 የ1954 ትርጉም) እርግጥ ነው፣ ይህ ምሳሌ ጠበኛ ለሆነ ባልም ይሠራል። በተጨማሪም መጽሐፍ ቅዱስ ልጆችን ማሳደግን በሚመለከት “ቅስማቸው እንዳይሰበር ልጆቻችሁን አታበሳጯቸው” ይላል። (ቆላስይስ 3:21) ሁልጊዜ ነቀፋ የሚሰነዘርባቸው ልጆች ወላጆቻቸውን በጭራሽ ማስደሰት እንደማይችሉ ሊሰማቸው ይችላል። እንዲያውም ወላጆቻቸውን ለማስደሰት ጥረት ማድረጋቸውን ከናካቴው ሊያቆሙ ይችላሉ።

ይህን ለማድረግ ሞክር፦ ለሚከተሉት ጥያቄዎች መልስ በመስጠት በቤተሰብህ ውስጥ መከባበር ይታይ እንደሆነ ገምግም።

በቤተሰቤ ውስጥ አለመግባባት ሲነሳ አብዛኛውን ጊዜ አንደኛው የቤተሰብ አባል ተናዶ ቤቱን ጥሎ ይወጣል?

የትዳር ጓደኛዬን ወይም ልጆቼን ሳነጋግር “ደደብ” ወይም “የማትረባ” እንደሚሉት ያሉ የስድብ ቃላትን መጠቀም ይቀናኛል?

ያደግኩት በሚሰዳደቡ ሰዎች መካከል ነው?

ቁርጥ ውሳኔ አድርግ። በአነጋገርህ አክብሮት ማሳየት የምትችልባቸውን አንድ ወይም ሁለት መንገዶች አስብና እንድትሠራባቸው ግብ አውጣ። (በንግግርህ ውስጥ “አንተ” ወይም “አንቺ” በማለት ፈንታ “እኔ” እያልክ ለመናገር ቁርጥ ውሳኔ አድርግ። ለምሳሌ ያህል፣ “አንቺ ሁልጊዜ . . .” ከማለት ይልቅ “እንዲህ ስትዪኝ ይከፋኛል” በል።)

ስላወጣኸው ግብ ለትዳር ጓደኛህ ለምን አትነግራትም? ከዚያም ከሦስት ወራት በኋላ ምን ያህል ለውጥ እንዳደረግህ ለማወቅ ጠይቃት።

ከልጆችህ ጋር ስትነጋገር የስድብ ቃላትን እንዳትጠቀም የሚረዱህን አንዳንድ መንገዶች አስብ።

ልጆችህን አመናጭቀሃቸው ወይም በሽሙጥ ተናግረሃቸው ከነበረ ለምን ይቅርታ አትጠይቃቸውም?

[በገጽ 6 ላይ የሚገኝ ሥዕል]

የውቅያኖስ ሞገድ ዐለትን እንደሚሸረሽር ሁሉ ጎጂ ቃላት የመሰንዘር ልማድም የቤተሰብን ትስስር ሊያዳክም ይችላል