አንደኛ ነገሥት 3:1-28

  • ሰለሞን የፈርዖንን ሴት ልጅ አገባ (1-3)

  • ይሖዋ ለሰለሞን በሕልም ተገለጠለት (4-15)

    • ሰለሞን ጥበብ ለማግኘት ጠየቀ (7-9)

  • ሰለሞን ሁለት እናቶችን ዳኘ (16-28)

3  ሰለሞን ከግብፁ ንጉሥ ከፈርዖን ጋር በጋብቻ ተዛመደ። የፈርዖንን ሴት ልጅ አገባ፤*+ እሷንም የራሱን ቤት፣ የይሖዋን ቤትና+ በኢየሩሳሌም ዙሪያ ያለውን ቅጥር+ ገንብቶ እስኪጨርስ ድረስ+ ወደ ዳዊት ከተማ+ አመጣት።  ሆኖም እስከዚያን ጊዜ ድረስ ለይሖዋ ስም የተሠራ ቤት ስላልነበረ+ ሕዝቡ መሥዋዕት ያቀርብ የነበረው ከፍ ባሉት የማምለኪያ ቦታዎች+ ላይ ነበር።  ሰለሞን መሥዋዕቶችንና የሚቃጠሉ መባዎችን ከፍ ባሉት የማምለኪያ ቦታዎች ላይ ከማቅረቡ በስተቀር በአባቱ በዳዊት ደንቦች መሠረት በመሄድ ይሖዋን እንደሚወድ አሳይቷል።+  ይበልጥ ታዋቂ* የሆነው ከፍ ያለ የማምለኪያ ቦታ ገባኦን ስለነበር ንጉሡ መሥዋዕት ለማቅረብ ወደዚያ ሄደ።+ ሰለሞን በዚያ መሠዊያ ላይ 1,000 የሚቃጠሉ መሥዋዕቶችን አቀረበ።+  በገባኦንም ይሖዋ ለሰለሞን ሌሊት በሕልም ተገለጠለት፤ አምላክም “እንድሰጥህ የምትፈልገውን ጠይቅ” አለው።+  በዚህ ጊዜ ሰለሞን እንዲህ አለ፦ “አገልጋይህ አባቴ ዳዊት በፊትህ በታማኝነት፣ በጽድቅና በቅን ልቦና ስለሄደ ጥልቅ የሆነ ታማኝ ፍቅር አሳይተኸዋል። በዙፋኑ ላይ የሚቀመጥ ልጅ በመስጠት እስከ ዛሬም ድረስ ለእሱ ይህን ጥልቅ የሆነ ታማኝ ፍቅር አሳይተሃል።+  አሁንም አምላኬ ይሖዋ ሆይ፣ እኔ ገና አንድ ፍሬ ልጅና ተሞክሮ የሌለኝ*+ ብሆንም አገልጋይህን በአባቴ በዳዊት ምትክ አንግሠኸዋል።  አገልጋይህ አንተ በመረጥከው፣+ ከብዛቱም የተነሳ ሊቆጠር በማይችለው ሕዝብ መካከል ይገኛል።  ስለሆነም አገልጋይህ ሕዝብህን መዳኘት እንዲሁም መልካምና ክፉ የሆነውን ነገር መለየት+ እንዲችል ታዛዥ ልብ ስጠው፤+ አለዚያማ ስፍር ቁጥር የሌለውን* ይህን ሕዝብህን ማን ሊዳኝ ይችላል?” 10  ሰለሞን ይህን መጠየቁ ይሖዋን ደስ አሰኘው።+ 11  ከዚያም አምላክ እንዲህ አለው፦ “ይህን ነገር ስለጠየቅክ እንዲሁም ለራስህ ረጅም ዕድሜ* ወይም ብልጽግና አሊያም የጠላቶችህን ሞት* ሳይሆን የፍርድ ጉዳዮችን መዳኘት እንድትችል ማስተዋልን ስለጠየቅክ+ 12  የጠየቅከውን አደርግልሃለሁ።+ ከአንተ በፊት ማንም ሰው ያልነበረውን+ ከአንተ በኋላም ማንም ሰው የማያገኘውን ጥበበኛና አስተዋይ ልብ እሰጥሃለሁ።+ 13  በተጨማሪም በሕይወት ዘመንህ* ሁሉ ከነገሥታት መካከል አንተን የሚተካከል እንዳይኖር+ አንተ ያልጠየቅከውን+ ብልጽግናና ክብር+ እሰጥሃለሁ። 14  አባትህ ዳዊት እንዳደረገው+ ሥርዓቶቼንና ትእዛዛቴን በመጠበቅ በመንገዶቼ ከሄድክ ረጅም ዕድሜም እሰጥሃለሁ።”*+ 15  ሰለሞንም ከእንቅልፉ ሲነቃ ሕልም መሆኑን ተረዳ። ከዚያም ወደ ኢየሩሳሌም ሄዶ በይሖዋ የቃል ኪዳን ታቦት ፊት ቆመ፤ የሚቃጠሉ መሥዋዕቶችንና የኅብረት መባዎችን+ አቀረበ፤ ለአገልጋዮቹም በሙሉ ግብዣ አዘጋጀ። 16  በዚህ ጊዜ ሁለት ዝሙት አዳሪዎች ወደ ንጉሡ መጥተው ፊቱ ቆሙ። 17  የመጀመሪያዋም ሴት እንዲህ አለች፦ “ጌታዬ ሆይ፣ እኔና ይህች ሴት የምንኖረው አንድ ቤት ውስጥ ነው፤ እሷም ቤት ውስጥ እያለች ልጅ ወለድኩ። 18  እኔ ከወለድኩ ከሦስት ቀን በኋላ ይህችም ሴት ልጅ ወለደች። ሁለታችን አብረን ነበርን፤ ከሁለታችን በስተቀር ቤቱ ውስጥ ማንም አብሮን አልነበረም። 19  ሌሊት ላይ ይህች ሴት ልጇ ላይ ስለተኛችበት ልጇ ሞተ። 20  ስለሆነም እኩለ ሌሊት ላይ ተነስታ እኔ አገልጋይህ ተኝቼ እያለሁ ልጄን ከአጠገቤ በመውሰድ በእቅፏ አስተኛችው፤ የሞተውን ልጇን ደግሞ በእኔ እቅፍ ውስጥ አስተኛችው። 21  እኔም በማለዳ ልጄን ለማጥባት ስነሳ ልጁ ሞቷል። ስለሆነም በማለዳ ብርሃን ልጁን ትክ ብዬ ስመለከተው እኔ የወለድኩት ልጅ አለመሆኑን ተረዳሁ።” 22  ሆኖም ሌላኛዋ ሴት “በፍጹም፣ በሕይወት ያለው የእኔ ልጅ ነው፤ የሞተው የአንቺ ልጅ ነው!” አለች። በዚህ ጊዜ የመጀመሪያዋ ሴት “በጭራሽ፣ የሞተው የአንቺ ልጅ ነው፤ በሕይወት ያለው የእኔ ልጅ ነው” አለች። እነሱም እንዲህ እያሉ በንጉሡ ፊት ተጨቃጨቁ። 23  በመጨረሻም ንጉሡ “ይህችኛዋ ‘ይህ በሕይወት ያለው ልጅ የእኔ ነው፤ የሞተው የአንቺ ልጅ ነው!’ ትላለች፤ ያቺኛዋ ደግሞ ‘በፍጹም፣ የሞተው የአንቺ ልጅ ነው፤ በሕይወት ያለው የእኔ ልጅ ነው!’ ትላለች” አለ። 24  ከዚያም ንጉሡ “እንግዲያውስ ሰይፍ አምጡልኝ” አለ። በመሆኑም ለንጉሡ ሰይፍ አመጡለት። 25  ንጉሡም “በሉ በሕይወት ያለውን ልጅ ለሁለት ሰንጥቁትና ግማሹን ለአንደኛዋ ሴት ግማሹን ደግሞ ለሌላኛዋ ስጡ” አለ። 26  በሕይወት ያለው ልጅ እናት ለልጇ ስለራራች ወዲያውኑ ንጉሡን “እባክህ ጌታዬ! በሕይወት ያለውን ልጅ ለእሷ ስጧት! በፍጹም አትግደሉት!” በማለት ተማጸነችው። ሌላኛዋ ሴት ግን “ልጁ የእኔም የአንቺም አይሆንም! ለሁለት ይሰንጥቁት!” ትል ነበር። 27  ንጉሡም መልሶ “በሕይወት ያለውን ልጅ ለመጀመሪያዋ ሴት ስጧት! እናቱ እሷ ስለሆነች በፍጹም አትግደሉት” አለ። 28  እስራኤላውያንም ሁሉ ንጉሡ የሰጠውን ፍርድ ሰሙ፤ ንጉሡ ፍትሐዊ ፍርድ መስጠት ይችል ዘንድ የአምላክን ጥበብ እንደታደለ+ ስለተመለከቱ ለንጉሡ አክብሮታዊ ፍርሃት አደረባቸው።+

የግርጌ ማስታወሻዎች

ወይም “ሴት ልጅ ወሰደ።”
ቃል በቃል “ታላቅ።”
ቃል በቃል “መውጫና መግቢያውን የማላውቅ።”
“አስቸጋሪ የሆነውን” ማለትም ሊሆን ይችላል። ቃል በቃል “ከባድ የሆነውን።”
ቃል በቃል “ብዙ ቀናት።”
ወይም “ነፍስ።”
ቃል በቃል “በቀኖችህ።”
ቃል በቃል “ቀናትህን አረዝማለሁ።”