እስካሁን የተማርከውን ወደኸዋል?
ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ተጨማሪ ትምህርት ማግኘት ትፈልጋለህ?
ይህ ጽሑፍ የያዘው ለዘላለም በደስታ ኑር!—አሳታፊ የመጽሐፍ ቅዱስ መማሪያ በተባለው መጽሐፍ ላይ ከሚገኙት በርካታ ርዕሰ ጉዳዮች ውስጥ ጥቂቶቹን ብቻ ነው።
ለመጽሐፉም ሆነ መጽሐፉን ተጠቅመን ለምንሰጠው ትምህርት ክፍያ አንጠይቅም። አንተ በሚመችህ ጊዜና ቦታ ልናስተምርህ ፈቃደኞች ነን።
ከምንሰጣቸው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርቶች መካከል የሚከተሉት ይገኙበታል፦
የሕይወት ዓላማ ምንድን ነው?
እውነተኛ ሰላም ማግኘት የሚቻለው እንዴት ነው?
የቤተሰብን ሕይወት አስደሳች ማድረግ የሚቻለው እንዴት ነው?
መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ወደፊቱ ጊዜ ምን ተስፋ ይሰጣል?